image
image
image
image
image

የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያው 6ወር ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና የቀሪ 6 ወራት የተከለሰ ዕቅድ ኦሬንቴሽን አደረገ።

ጥር 7, 2017
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዮዲት ሰለሞን እንደገለጹት የውስጠ ፓርቲ ስራዎች ለማጠናከር በየግዜዉ የሚሰጡ የኢንስፔክሽን ስነ ምግባር ኮሚሽን ግብር መልስ መነሻ ያደረጉ ስራዎች በትኩረት በመስራት አሰራር ከማስጠበቅ አንጻር ሚናው የላቀ እንደሆነ ጠቅሰዋል። የወረዳው ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ አይቼሽ አዲስ እንደገለጹት በ6 ወራት ዉስጥ ያከናወናቸውን በርካታ ተግባራት ከኮሚሽን ህብረት ኮሚቴና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመቀናጀት ከተደራጀበት አላማ አንጻር በአፈጻጸም ደረጃ የተሻለ ቢሆንም አሁንም ግን ዉስንነቶች እንዳሉና በቀጣይ መታረም እንዳለባቸው ኃላፊዋ ጠቁመዋል። ጥያቄዎቹንና አስተያየቶች መነሻ በማድረግ የኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዋ እንደገለጹት በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲ አባላትና አመራሮች ጨምሮ ፓርቲው ባስቀመጠው የአሰራርና አደረጃጀት፣ መመሪያዎችን የመጠበቅና የማስጠበቅ ሙሉ ኃላፊ ነት እንዳለው የተገለጸ ሲሆን በመጨረሻም የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ዉይይቱን አጠናቅቀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች