የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
-
የተቋም አቅም ግንባታ ስራን የሚያሳልጡ ዘመናዊ አሰራሮችንና ተሞክሮዎችን በመለየት በክ/ከተማ አስተዳደሩ መስሪያ ቤቶች ላይ ተግባራዊ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ አፈፃፀሙን ይከታተላል፣ አስፈላጊዉን የቴክኒክና የሙያ ድጋፍ ይሰጣል፤
- በመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰዉ ሀብት ልማት በቀጣይነት የሚለማበትንና ጥቅም ላይ የሚዉልበትን ስርዓት ይዘረጋል፤ ይተገብራል፤ እንዲተገበር ያደርጋል፤
- በክ/ከተማው አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ተገቢዉ ስታንዳርድ መኖሩን ያረጋግጣል፤ እንዲያዘጋጁ ያደርጋል፤ ያጸድቃል፤ ተግባራዊ መደረጉን ያረጋግጣል፤
- በከተማው አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የአገልግሎት አሰጣጥ አፈጻፀም ይከታተላል፣ የተገልጋዩን እርካታ ጥናት ያካሂዳል፣ የጥናቱን ውጤት ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፤
- የመንግስት ሰራተኞች ቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለዉ መንገድ መዘርጋቱንና ተግባራዊ መደረጉን እንዲሁም ዉጤታማነቱን ያረጋግጣል፤
- ያልተማከለ የአስተዳደር ስርዓትን ለማጠናከር የሚያስችል የማስፈጸም አቅም ግንባታ ይዘረጋል፣ አፈጻጸሙንም ይከታተላል፣ ይደግፋል፤
- የመንግስት ሰራተኞችን ወቅታዊ አፈፃፀም ምዘና የአሰራር ስርዓት ይዘረጋል፤ ተግባራዊነቱንም ያረጋግጣል፤
- የመንግስት ሰራተኛ በብቃትና በአፈጻፀም ላይ የተመሰረተ የምደባ፣ የደረጃ ዕድገትና የእርከን ጭማሪ፣ የጥቅማጥቅምና የማበረታቻ ስርዓት ይዘረጋል፣ እንዲተገበር ያደርጋል፤ ውጤታማነቱን ይገመግማል፣ አስፈላጊዉን የማሻሻያ እርምጃ ይወስዳል፤
- የመንግስት ሰራተኞች አቀጣጠር፣ አመዳደብ፣ የደረጃ እድገት፣ ዝውውር፣ አበልና ጥቅማ ጥቅም፣ ስልጠናና የዲሲፕሊን አፈጻጸም በህግ መሰረት መፈጸሙን ይከታተላል ያረጋግጣል፤
- በህግ መሰረት የከተማ አስተዳደሩን የመንግስት ሰራተኞችን ከጡረታ ዕድሜ ክልል በላይ በአገልግሎት ላይ ለማቆየት በሚቀርብ ጥያቄ ተቀብሎ ዉሳኔ ይሰጣል ለሚመከታወ አካል ያቀርባል፤
- የክ/ከተማ አስተዳደሩን የሰዉ ሀብት መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ያደራጃል፤
- የህዝብ አገልጋይነት አስተሳሰብ ያለዉ አመራርና ፈጻሚ ይገነባል እንዲገነባ ይሰራል፣ የብቃት ማረጋገጫ ስርዓት ተግባራዊነቱንም ይከታተላል፣ ይደግፋል፤ ያረጋግጣል፤
- በሚዘረጋቸው አዳዲስ አሰራሮች፤ አደረጃጀቶችና ማኑዋሎች ዙሪያ አጫጭር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን ይሰጣል፣ እንዲሰጥ ያደርጋል፤ ፣
- ሁሉም ተቋማት ዉጤታማ አፈጻፀም እንዲኖራቸዉ የሚያደርጋቸዉን አዳዲስ የለውጥ መሳሪያዎች ከራሳቸዉ ባህርይ አንጻር አጥንተው እንዲያቀርቡ ያበረታታል፤ ሲጸድቅም ተግባራዊ መሆኑን ይከታተላል፣፤
- የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሪፎርምና አገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸም ውጤታማነት ይመራል፣ አፈጻጸማቸውን ይገመግማል፣ ግብረ- መልስ ይሰጣል፣ ደረጃ ያወጣል፣ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ይልካል፣
- ከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ላይ የሰራተኞች አፈጻጸም ምዘና ተግባራዊ እንዲሆን ሥርዓት ይዘረጋል፣ አፈጻጸሙን በመፈተሸ ግብረ-መልስ ይሰጣል፣ የምዘና ሂደቱ በበላይነት ያስተባብራል፣ ያረጋግጣል፡፡