image
image
image
image
image

የመጀመሪያ ሩብ አመት አገልግሎት አሰጣጥና ሪፎርም የሴክተሮች አፈፃፀም ላይ በመነሳት ስልጠናዊ ግምገማ ከስራ ሂደቶችና ከቡድን መሪዎች ጋር ተካሄደ፤

ጥቅምት 2, 2017
(ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት፣ ጥቅምት 2018 ዓ.ም.) የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ደበላ፣ ወረዳው በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ባስመዘገበው የአገልግሎት አሰጣጥና ሪፎርም አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ስልጠናዊ ግምገማ እና የመማክርት ጉባኤ ማካሄዱን አስታውቀዋል። አቶ ስንታየሁ እንደገለጹት፣ መድረኩ የተዘጋጀው በወረዳው የሚገኙ የሴክተር ጽ/ቤቶች የአንደኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀማቸውን በመገምገም፣ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የለውጥ አቅጣጫዎችን ለመቀየስ ነው። እያንዳንዱ የሥራ ዘርፍ (ሴክተር) በሩብ ዓመቱ ያከናወናቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ሥራዎች፣ የሪፎርም ዕቅዶች አፈፃፀም፣ እና የህዝብ እርካታ ደረጃ ተገምግሟል። በመገምገሚያው ወቅት የተለዩ ጥንካሬዎችና ክፍተቶች ለሚመለከታቸው ቡድን መሪዎች በዝርዝር ቀርበዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች