Welcome to Lideta Subcity Woreda 6 Administration!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር በሰላም መጡ!       Baga Gara Kutaa Magaalaa Lidetaa Aanaa 6 Nagaan Dhuftan!

የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት

የክ/ከተማችን ብሎም የወረዳችን ነዋሪ ፈጣን፣ ተደራሽ እና ጥራት ያለው አገልግሎት የማግኘት መብት ያለው በመሆኑ ይህንን የህዝባችንን ፋላጎት ዕውን ከማድረግ አኳያ የአገልገሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ዘመናዊ ማድረግ እንዲሁም ቀጣይነት ባለው መልኩ ራሱን እያሻሻለ እና እያሰደገ የሚሄድ በስነምግባሩ የተመሰገነ፣ ነፃ ገለልተኛ የሆነ ፐብሊክ ሰርቪስ መፍጠር ዋነኛው ጉዳይ ሊሆን ይገባል፡፡

የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት በወረዳው የሚገኙ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለዉጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በስነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰዉ ኃይል እንዲመራ የማድረግ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የህዝቡን የመገልገል መብቶች በተሟላ ሁኔታ በማስጠበቅ የዜጎች.... ተጨማሪ ያንብቡ

አቶ ስንታየሁ ደበላ , የልደታ ወረዳ 6 ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
image description

ዋና ዋና አገልግሎቶች

የሰው ሀብት ክትትልና ድጋፍ አገልግሎት
የሰው ሀብት ስምሪት እና መረጃ አግልግሎት
የሰው ሀብት ኦዲት አገልግሎት / HR Audit Services
የሰው ሀብት ቅሬታና አቤቱታ አገልግሎት
የሰው ሀብት ልማትና ብቃት ማረጋገጫ አገልግሎት
የወረዳ ማሰፈጸም አቅም ግንባታ አገልግሎት
የአገልግልት ስታንዳርዳይዜሽንና ምዘና አገልግሎት
የሪፎርም ክትትልና ድጋፍ አገልግሎት

የጽ/ቤቱ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች

ዜና | Oduu | News
"ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር እና የሰራተኛውን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው።"- ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ

የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ለሰራተኛውና ለተገልጋዮች ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ ደረጃቸውን የጠበቁ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ስራ አስጀመረ። በዚህ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ አጠቃላይ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ዘላቂ እና ጠንካራ ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለው ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር እና የሰራተኛውን እውቀት በአግባቡ በመጠቀም የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። አስተዳደሩ፤ በላቀ ትጋትና ቁርጠኝነት ህዝብን በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ልዕልቲ ሰራተኞች ደግሞ በታማኝነትና በቅንነት ህዝቡን እንዲያገለግሉ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል። የመንግስት ሰራተኞችን የኑሮ ጫናን ለማቃለል በመንግስት በኩል የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በስራው አከባቢ ያለአንዳች እንግልት አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችሉ ሰራተኛው አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች በቅረብ እንዲያገኝ ያስችላል ብለዋል። በዚህ መርሀ ግብር ላይ የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማሳለጥ የሚያስችሉ ደረጃቸውን የጠበቁ ቴክኖሎጅዎችን ስራ ማስጀመሩን ወ/ሮ ልእልቲ አያይዘው ገልፀዋል። በዛሬው ዕለት ደረጃውን የጠበቀ የስፖርት ማዕከል፣ ሱፐር ማርኬት፣ የህፃናት መጫዎቻ ስፍራ፣ የመጀመሪያ ህክምና አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ ቤተ-መጽሃፍት እና ሌሎችንም አገልግሎቶች ስራ አስጀምሯል። በተያያዘ አስተዳደሩ ስታንዳርዱን የጠበቀ የወረፋ ማስጠበቂያ፣ የውስጥና የውጭ ካሜራ መቆጣጠሪያ ሴንተር፣ ዲስፕሌዮች፣ ዲጅታል ዙም ሚቲንግ፣ QR ኮድ ያለው የሰራተኞች ባጅና ሌሎችንም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ተግባር አስገብቷል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
የባለ ጉዳይ ቀን የአገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደረገ።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የዕለተ አርብ የባለጉዳይ ቀን የሴክተር ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደርጓል። በምልከታው ጥቅል የየተቋማቱ የስራ ስምሪት እና የባለጉዳይ አያያዝ ታይቷል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
'ከጂኦ-ስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና': የባህር በርና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳዮች ውይይት ተደረገ።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች "ከጂኦ-ስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ወቅታዊ ሀገራዊና ዓለም አቀፍ አጀንዳዎችን በማንሳት ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱ ሀገራዊ ስኬቶችን በመገንዘብ እና ብሔራዊ ጥቅምን በማስከበር ላይ ያተኮረ ነበር። የመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዮዲት ሰሎሞን፣ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የሀገርን ከፍታ የሚያረጋግጡ በርካታ ስኬታማ ተግባራት ደረጃ በደረጃ እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል። ሁሉም የመንግስት ሰራተኛ ይህንን ታሪካዊ ወቅት ተገንዝቦ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። ወ/ሮ ዮዲት አክለውም፣ በእድገት ጎዳና ላይ የምትገኘው ሀገራችን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የተሰራውን ታሪክ፣ በባህር በር ጉዳይም ላይ መድገም እንደሚገባት አጽንኦት ሰጥተዋል። ይህንን ለማሳካት ሰራተኛው የስነ ልቦና የበላይነትን በመያዝ በብሔራዊ ጥቅም ላይ በጋራ መቆም እንዳለበት አስገንዝበዋል። የባህር በር ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ መልስ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የመንግስት ሰራተኛው በቁጭት በጋራ መቆም እንደሚገባ አሳስበዋል። በመድረኩ ለውይይት መነሻ ሆኖ የቀረበው ሰነድ በብሔራዊ ጥቅምና በጂኦ-ስትራቴጂያዊ ቁመና ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፣ ሀገራዊና ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን ዳስሷል። ሰነዱን ያቀረቡት የወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ደበላ ናቸው። የውይይት መድረኩን የመሩት የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ም/ፓርቲ ኃላፊና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳምጠው ወንታሞ ሲሆኑ፣ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገራዊ ስብራቶች በመጠገናቸው ኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። አቶ ዳምጠው አክለውም፣ ትናንት አባቶቻችን ያስረከቡንን ታላቅ ሀገር ክብሯንና ታላቅነቷን በተጠበቀ መንገድ ለልጆቻችን እና ለሚመጣው ትውልድ ለማስረከብ በመንግስትና በህዝብ ርብርብ ወደ ቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እየተመለሰች መሆኑን አስገንዝበዋል። ውይይቱ ከተካሄደ በኋላ አስተያየት የሰጡ የመንግስት ሰራተኞች በበኩላቸው፣ እንደ መንግስት ሰራተኛ ውስጣዊ አንድነታችን በማጠናከር ጂኦ-ስትራቴጂያዊ ቁመናችን በመግናጸፍ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር በጋራ እንቆማለን ሲሉ ገልጸዋል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
የመጀመሪያ ሩብ አመት አገልግሎት አሰጣጥና ሪፎርም የሴክተሮች አፈፃፀም ላይ በመነሳት ስልጠናዊ ግምገማ ከስራ ሂደቶችና ከቡድን መሪዎች ጋር ተካሄደ፤

(ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት፣ ጥቅምት 2018 ዓ.ም.) የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ደበላ፣ ወረዳው በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ባስመዘገበው የአገልግሎት አሰጣጥና ሪፎርም አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ስልጠናዊ ግምገማ እና የመማክርት ጉባኤ ማካሄዱን አስታውቀዋል። አቶ ስንታየሁ እንደገለጹት፣ መድረኩ የተዘጋጀው በወረዳው የሚገኙ የሴክተር ጽ/ቤቶች የአንደኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀማቸውን በመገምገም፣ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የለውጥ አቅጣጫዎችን ለመቀየስ ነው። እያንዳንዱ የሥራ ዘርፍ (ሴክተር) በሩብ ዓመቱ ያከናወናቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ሥራዎች፣ የሪፎርም ዕቅዶች አፈፃፀም፣ እና የህዝብ እርካታ ደረጃ ተገምግሟል። በመገምገሚያው ወቅት የተለዩ ጥንካሬዎችና ክፍተቶች ለሚመለከታቸው ቡድን መሪዎች በዝርዝር ቀርበዋል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ወረዳ 06 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን የአገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተካሄደ።

በመልካም አስተዳደርና ግልጽነት መርህ መሠረት የዜጎችን አገልግሎት አሰጣጥ ለማረጋገጥ ያለመ የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ አድርጓል። ምልከታው የተካሄደው በአስተዳደሩ ሥር የሚገኙ ሴክተር ተቋማት (ጽ/ቤቶች) በሚሰጡት አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ነው። በምልከታው ሂደት በወረዳ አስተዳደሩ ሥር የሚገኙ የሴክተር ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ባለጉዳይን የሚያስተናግዱበት አግባብ ላይ ጥልቅ ቅኝት ተደርጓል።

image
image
image

አቅጣጫ ጠቋሚ

በወረዳዉ ህንፃ ዉስጥ ያሉ ፅህፈት ቤቶች አቅጣጫ ጠቋሚ

ህንፃ ቁ1 ምድር ላይ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

የውስጥ ኦዲት ጽ/ቤት

ሴቶች ፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት

ፋይናንስ ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ1 አንደኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ከተማ ግብርና ጽ/ቤት

ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት

ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ2 ምድር ላይ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ንግድ ጽ/ቤት

ገቢዎች ቅ/ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ2 አንደኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ስራና ክህሎት ጽ/ቤት

ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ2 ሁለተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ2 ሶስተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት

ህብረት ስራ ጽ/ቤት

ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ2 አራተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ትምህርት ጽ/ቤት

ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ኢንስፔክሽን እና ስነ ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት

ህንፃ ቁ3 ምድር ላይ የሚገኙ

አዳራሽ

በልደታ ክ/ከተማ የወረዳ 6 ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለውጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በሥነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰው ኃይል እንዲመራ በማድረግ ለተገልጋዮቹ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዲስ መልክ በመለየት አደራጅቷል፡፡

በተጨማሪም በጽ/ቤት የሚሰጠው አገልግሎት የተገልጋይ ፍላጎትን ማዕከል አድርጎ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች፣ አገልግሎቱ የሚሰጥበት ስታንዳርድ፣ የሚሰጥበትን ቦታ እና ከተገልጋይ የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎችን በግልጽ በዝርዝር በማስቀመጥ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ፍህታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና ተገልጋዮች ምን ዓይነት አገልግሎት በምን ዓይነት ደረጃ ማግኘት እንደሚገባቸው ግንዛቤ በመፍጠር በዚህም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲያብብ ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂት ለመፍታት በምናደርገው ጥረት ባለድርሻ አካላትና ህብረተሱቡ ከጽ/ቤቱ ጎን እንዲቆሙ እናሳስባለን፡፡